ONE BIBLE TRUTH /የእወነት ቃል /
ለፍጥረቱ የበኵራት ዓይነት እንድንሆን በእውነት ቃል አስቦ ወለደን

ኢየሱስ ራሱ እግዚአብሔር ነው፤ ወደ ማን ይማልዳል?

ኢየሱስ ራሱ እግዚአብሔር ነው፤ ወደ ማን ይማልዳል?

 
ኢየሱስ ራሱ እግዚአብሔር ነው፤ ወደ ማን  ይማልዳል?”
በቃላት  መዋጋትን  እንደ  በሽተኛ  የሚናፍቁ  ወገኖች፥  ቅዱሳት  መጻሕፍት  ስለክርስቶስ መካከለኛነት  በግልጽ  የሚያስተምሩትን  ትምህርት  በመጽሐፍ  ቅዱስቃል  ማስተባበል ሲያቅታቸው፥  በምስጢረ  ሥላሴ  ላይ  ትልቅ  ተፋልሶንየሚያስከትል መሠረተ ቢስ አመክንዮንያቀርባሉ፤ እንዲህ በማለት፥ ‘ኢየሱስ ራሱእግዚአብሔር ነው ወደ ማን ይማልዳል?’ እንዲህ ባዮቹ፥ኢየሱስን ከመካከለኛነቱ ስፍራ  ለማንሣት  ሲሉ  ይህን  ጥያቄ  እንደሚያነሡት  ይታወቃል።
ኢየሱስ ራሱ እግዚአብሔር ነው ወደ ማን ይማልዳል?’ ለሚለው ጥያቄ መልሱ ወደ አብ የሚልይሆናል። ከፍ ብለን እንደ ተመለከትነው ራሱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
አብን እለምናለሁ” ሲል ተናግሯል (ዮሐ. 1415)
ኢየሱስ ስለ ደቀ መዛሙርቱ ወደ አብ እንደሚለምን በተደጋጋሚ ተናግሯል  (ዮሐ.1415-16 17920-21)  የሚለምነው  ኢየሱስ  ነው፤  የሚለምነው  ስለ  ደቀ መዛሙርቱ ነው፤ የሚለምነውአብን ነው። እግዚአብሔር በሾመው በመካከለኛችን በክርስቶስ ስፍራ የራሳቸውን መካከለኛያስቀመጡ ሰዎች፥  “እርሱ  (ኢየሱስራሱ እግዚአብሔር  ነው  ወደ  ማን  ይለምናል?”  ሲሉ ለሚያቀርቡት  ጕንጭ  አልፋ ክርክር፥  ይህ  የጌታችን  ንግግር  በቂ  ምላሽ  ነው።  ይህን  ትምህርት ለማረጋገጥ ከእርሱ በላይ ከቶ ማን ይመጣል?
በዚህ  ከንቱ  የክርክር ጭብጥ  እንደሚረቱ ሲያውቁ፥  “እለምናለሁ ቢልም  እንዲህ ያለው እስከ ሞቱድረስ ነው፤ ከዚያ በኋላ ግን አይለምንም” ሲሉ ከፍለው ያምናሉ። ይሁን  እንጂ  ጌታ  ኢየሱስ  በአብ ቀኝ  ከተቀመጠ  በኋላም  መካከለኛችን  ነው።  ለምሳሌ፡-  ከመሰቀሉ  አስቀድሞ፥  “ብትወዱኝ ትእዛዜን  ጠብቁ፤  እኔም  አብን እለምናለሁ፤  ለዘላለምም  ከእናንተ ጋር  እንዲኖር ሌላ  አጽናኝይሰጣችኋል” ሲል አብን እንደሚለምን ተናግሯል። ወደ ሰማይ ካረገና በእግዚአብሔር ቀኝከተቀመጠ በኋላ  ደግሞ  በእርሱ  መካከለኛነት  በኩል  የመንፈስ  ቅዱስ  ስጦታ ለሐዋርያትተሰጥቷል።
በተለይ  ከትንሣኤው  በኋላ  በኢየሱስ ስም  አብን  ስንለምን፥  ደስታችን  ፍጹም  ይሆናል፤  እንደ እግዚአብሔር  ፈቃድ የምንለምነውን  እንቀበላለን፤  በኢየሱስ  ስም  ስንለምን  እርሱ  አብን አይለምንም፤ኢየሱስ  ክርስቶስን  ስለምንወደውና  በስሙ  ስለምናምን  አብ  ይወደናልና፥  በስሙያቀረብነው ልመና ተቀባይነት ይኖረዋል። አንድምታ ወንጌሉ ለዚህ ንባብ የሰጠው ትርጓሜ እንዲህይላል፤ “በቅንው ወልድከ /በተቸነከረው ልጅህ/ በስቁል ወልድከ /በተሰቀለው  ልጅህ/  እያላችሁ አብን  ብትለምኑት  የለመናችሁትን  ሁሉ እንዲያደርግላችሁ  በውነት  እነግራችኋለሁ።” ኢየሱስራሱ  በስሙ  የምንለምነውን  ሁሉ እንደሚያደርግልን ተናግሯል (ዮሐ. 1413-14) ከዚህ  ቃል ጋር  የሐዋርያው  የጳውሎስ መልእክትም  ይስማማል፤  “እግዚአብሔር አብን  በእርሱ  [በኢየሱስእያመሰገናችሁ፥  በቃል  ቢሆን  ወይም  በሥራ የምታደርጉትን  ሁሉ  በጌታ  በኢየሱስ  ስም አድርጉት”  (ቈላ.  317)  ስለዚሀ ምስጋና፣  ጸሎት፣ ልመና  ከክርስቲያኖች ወደ እግዚአብሔር የሚቀርበው  በኢየሱስ ስም  አማካይነት  ነው  (ሮሜ  18  725 ኤፌ.  321  520) እግዚአብሔርም ሕዝቡን  የባረከውና  የሚባርከውም  በኢየሱስ  ክርስቶስ  አማካይነት  ነው  (.. 326 ኤፌ. 13) በቅዳሴ  እና  በአበው  ጥንታውያን  ጸሎቶች    ውስጥም  ይህን  በግልጽ ማስተዋል ይቻላል።  ለምሳሌ፡-  በቅዳሴ  ላይ  “ነአኵተከ  እግዚኦ  በፍቁር  ወልድከ  እግዚእነኢየሱስ  - አቤቱ  በተወደደው ልጅህ  በጌታችን  በኢየሱስ  [ስምእናመሰግንሃለን።” የሚልና በኢየሱስ  ክርስቶስ  በኩል  ለአብ  የቀረበ  ምስጋና  እናገኛለን።  ሊጦን፣ መስተብቊዕ፣  ዘይነግሥ፣ የተባሉት  ጸሎቶች  የሚደመደሙት  “በአሐዱ  ወልድከ እግዚእነ ኢየሱስ  -  በአንድ  ልጅህ በጌታችን  በኢየሱስ”  በሚለው  የኢየሱስን  ስም
ምዕራገ  ጸሎት  (ጸሎት  ማሳረጊያ)  አድርገው  ነው።  ያለ  እርሱ  ስም  ጸሎትም ልመናም ወደ አብየሚያርግበት መንገድ ከቶ የለምና።ኢየሱስ በመጸለይ፣ በመለመንና በመማለድ መካከለኛነቱንአሳይቷል ጌታችን  ኢየሱስ  ክርስቶስ  በሰው  እና  በእግዚአብሔር መካከል  ያለው መካከለኛ እርሱብቻ  ስለ ሆነ፥  በእርሱ  በኩል  በስሙ  እንዲጸለይ ማስተማር ብቻ  ሳይሆን፥ በዚህ ምድር ላይ በሥጋሲመላለስ በነበረ ጊዜ፥ እርሱ ራሱ ስለ ሌሎች በመጸለይና እግዚአብሔርን በማመስገን ጭምርመካለኛነቱን በተግባር አሳይቷል። ለለምሳሌ፡ስለ ደቀ መዛሙርቱ  (ማቴ.  1125)  በአልዓዛርመቃብር  ላይ  (ዮሐ.  1141-42) እግዚአብሔርን  አመስግኗል።  ብቻውን፥  አንዳንድ  ጊዜም  ከደቀ መዛሙርቱ አንዳንዶችን ይዞ ጸልዮአል  (ማቴ.  1423  2636-46 ማር.  135 ሉቃ.  928ዮሐ. 1228 171-26)     ሊቀ  ካህናት  ኢየሱስ  ክርስቶስ  በአንዳንድ  ክፍሎች  መጸለዩ  ብቻ  ሲጠቀስ፥በአንዳንዶቹ  ክፍሎች  ደግሞ  የጸለየባቸው  ርእሰ  ጕዳዮችና  የጸለያቸው  ጸሎቶች ተመዝግበዋል። በዋናነት  የሚጠቀሰው  ጸሎቱ  በዮሐንስ  ወንጌል ምዕራፍ  17  ላይ የሰፈረው  ጸሎቱ  ነው።  ይህ የሊቀ  ካህናትነቱ  ጸሎት  በአጠገቡ  ለነበሩ  ደቀ መዛሙርቱ  ብቻ  ሳይሆን  ወደ  ፊት  እስከ  ዓለም ፍጻሜ  ድረስ  በእነርሱ  ስብከት መሠረት በእርሱ ለሚያምኑት ሁሉ  የቀረበ  የምልጃ ጸሎት  ነው። “እኔ ስለ እነዚህ እለምናለሁ፤  ስለ  ዓለም  አልለምንም  ስለ  ሰጠኸኝ  እንጂ፤  የአንተ  ናቸውና፤  …ሁሉም አንድ ይሆኑ ዘንድ፥ ከቃላቸው የተነሣ በእኔ ስለሚያምኑ ደግሞ እንጂ ስለ እነዚህ ብቻአልለምንም፤” የሚለው ይህን ያመለክታል (ዮሐ. 17920-21)  ሰይጣን  ሐዋርያትን  እንደ  ስንዴ ሊያበጥራቸው  በወደደ  ጊዜ፥  ጌታችን  ኢየሱስ ክርስቶስ በተለይ ለስምዖን ጴጥሮስ አማልዶ  ነበር፤ቃሉም  “… እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ  ስለ  አንተ  አማለድሁ”  ይላል  (ሉቃ.  2231)  ጌቴ ሴማኒ  በተባለች የአትክልት  ስፍራም  ተንበርክኮ  ሲጸለይ፥  “አባቴ፥  ቢቻልስ፥  ይህች  ጽዋ  ከእኔትለፍ፤  ነገር  ግን  አንተ  እንደምትወድ  ይሁን  እንጂ  እኔ  እንደምወድ  አይሁን አለ” (ማቴ. 2639-42) በመጨረሻም ለሰቀሉት ሰዎች አባት ሆይየሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸውሲል ወደ አባቱ ጸልዮላቸዋል (ሉቃ. 2334) ይህ ትክክል ነው፤ ነገር ግን በሥጋው ወራት የተደረገነው እንጂ ከትንሣኤው በኋላ እርሱ  መካከለኛ  አይደለም  የሚሉ  አንዳንዶች  ይኖራሉ። 
የክርክራቸው  ግብም
የመካከለኛነትን ግብር ከእርሱ ላይ አንሥቶ ለሌሎች መስጠት ነው። ለጊዜው ግን፥ እርሱን መካከለኛማለት  ክብሩን  ዝቅ ማድረግ  ነው  የሚል  የመከራከሪያ ጭብጥ ያቀርባሉ። ኢየሱስ በሥጋውወራት የእርሱ ስለ ሆኑት በመጸለዩ ከአምላክነቱ ደረጃ ዝቅ  ብሏል  አያሰኝም።  ‘አንድ  ጊዜ ባቀረበው  ምልጃና  መሥዋዕት  ዛሬም መካከለኛችን እርሱ ብቻ  ነው፤ ሌላ  የሚተካው መካከለኛ የለም’ ማለትም ከክብሩ ዝቅ  የሚያደርገው  ሳይሆን፥  ትክክለኛ  የዐዲስ  ኪዳን  ሊቀ  ካህናትነቱን የሚያሳይ ነው። ከዚህ  ዕትም በፊት በወጡት ተከታታይ ጽሑፎች  ላይ እንደ ተጠቀሰውም፥ሐዋርያት  በመልእክቶቻቸው  ኢየሱስ  ከሙታን  ተለይቶ  ከተነሣና  በአብ  ቀኝ ከተቀመጠ በኋላምመካከለኛ መሆኑን መጻፋቸውን ገልጸናል።  
ነገር  ግን  በቀደመ  ልመናውና ምልጃው  ዘወትር  በአዳኝነቱ  አምነው  በስሙ  እየጸለዩ የሚመጡትን  ወደ እግዚአብሔር የሚያቀርባቸውና የሚያድናቸው ግን እርሱ ብቻ ነው። “… እርሱግን ለዘላለም  የሚኖር  ስለ  ሆነ  የማይለወጥ  ክህነት  አለው፤  ስለ  እነርሱም  ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት  ይኖራልና  ስለዚህ  ደግሞ  በእርሱ  ወደ  እግዚአብሔር የሚመጡትን  ፈጽሞ ሊያድናቸው  ይችላል።”  (ዕብ.  725)   ለዘላለም  እንዳቀረበና    አንድ  ጊዜ  የቀረበው መሥዋዕት  ለዘላለም እንደሚያገለግልና ለኀጢአት ሁሉ የቀረበ መሆኑን ከተረዳን (ዕብ. 101214)ስለ ሁላችን  አንድ  ጊዜ  ያቀረበው  ምልጃም  (ዮሐ.  1720-21)  ለዘላለም  እንደሚሠራ መረዳት አያዳግተንም።  ይህን  ወደ  ጎን  ጥለንና  ለኢየሱስ  ክብር  የምንከራከር መስለን  በእርሱ  ስፍራ ሌሎች  መካከለኞችን  ለማስቀመጥ  በማሰብ  የክርስቶስን መካከለኛነት  ማስተሐቀር  (ማቃለልግን  ትልቅ  ስሕተት  ነው።  እግዚአብሔር የሾመልንን የታመነ፣ የሚምርና የሚራራ ሊቀ ካህናትላለመቀበል መወሰናችንንም ያስረዳል።
 
የክርስቶስን  መካከለኛነት  በተሳሳቱ  ምድራውያን  አመለካቶች  ላይ  መመሥረት የለብንም። አንዱ  ምድራዊ  አመለካከት  የሚለምን  የበታች፥  የሚለመን  ደግሞ የበላይ ተደርጎ መወሰዱ ነው።ክርስቶስ አብን መለመኑ፥ አብ በክርስቶስ መለመኑ የበታችነትንና  የበላይነትን አያሳይም። የእግዚአብሔርና  የሰው  ዕርቅ  የተከናወነው በእግዚአብሔር  ፍቅርና  በጎ  ፈቃድ  ላይ ተመሥርቶ  ነው።  ሰው  እግዚአብሔርን ፈልጎትና ልታረቅህ ብሎት አማላጅም ልኮ ዕርቅአልጠየቀውም። ወደ ገዛ መንገዱ ያዘነበለውንና በኀጢአቱ ምክንያት ሞት የተፈረደበትን ሰው ከራሱጋር ሊያስታርቅ የወደደው  ራሱ  እግዚአብሔር  ነው።  “በእርሱ  የሚያምን  ሁሉ  የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው  እንጂ  እንዳይጠፋ  እግዚአብሔር  አንድያ  ልጁን  እስኪሰጥ  ድረስዓለሙንእንዲሁ ወዶአልና”  (ዮሐ. 316) በተባለው መሠረትም፥ በእርሱና በሰውመካከል ሊከናወንስለሚገባው ዕርቅ አስታራቂ አድርጎ የላከውና ዓለሙን ከራሱ ጋርያስታረቀው  በአንድ  ልጁ በጌታችን  በኢየሱስ  ክርስቶስ  ነው  (ሮሜ  510  2ቆሮ.518-19 ኤፌ. 216) ይህምየእግዚአብሔርና የሰው ዕርቅ በክርስቶስ ሞት ስለተከናወነ፥  ከዚህ  በኋላ  ከሰው  የሚጠበቅ  ሌላ የመታረቂያ  መንገድ  የለም፤  ሰውኀጢአተኛ መሆኑን ተገንዝቦ፥ ንስሓ ገብቶና በክርስቶስየተከናወነውን ዕርቅ አምኖወደ እግዚአብሔር ሊቀርብ ይችላል፤  “በእርሱ ሥራ ሁላችን በአንድመንፈስ ወደ አብ መግባት አለንና” ተብሎ እንደ ተጻፈ (ኤፌ. 218)   
  ((((((((((((((አብ አማላጅ ተብሏልና ወደ ማን ይማልዳል?))))))))))))))))
እነዚሁ ወገኖች  “አብ አማላጅ ተብሏልና ወደ ማን ይማልዳል?” ሲሉ ለሚያነሡት ጕንጭ አልፋክርክር የሚያቀርቡት ሌላው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ፥ “አባቶቻችሁ ከግብጽ  ምድር  ከወጡበት  ቀን ጀምሮ  እስከ  ዛሬ  ድረስ፥  በየዕለቱ  እየማለድሁ ባሪያዎቼን  ነቢያትን ሁሉ ልኬባችሁ  ነበር” የሚለውን  ነው  (ኤር.  725)    በዚህ የእግዚአብሔር  ንግግር ውስጥ  “እየማለድሁ”  የሚለውቃል  አብ  አማላጅ መሆኑን ያሳያል የሚል ነው ክርክሩ። ይሁን እንጂ በዐማርኛ ማለደ የሚለው ቃልመለመንን ብቻ  ሳይሆን  በጥዋት መነሣትንም  የሚያመለክት  ቃል  ነው  (መዝ.  578 መዝ. 1082 ማር. 135 ሉቃ. 2138) በትንቢተ ኤርምያስ ምዕራፍ 7 ቊጥር 25 ላይ የተጠቀሰው ቃል  የሚናገረውም  በማለዳ  መነሣትን  (ከጥንቱ  ከጥዋቱ  ጀምሮ መናገሩን)  እንጂ ምልጃማቅረብን  አይደለም።  ከሚከተሉት  የትንቢተ  ኤርምያስ ክፍሎች ጋር ይህን ክፍል ብናስተያየውምጕዳዩ በጥዋት መነሣትን እንጂ ምልጃን (ልመናንፈጽሞ አያሳይም  (ኤር. 73 113 2652919 3233 3514 15 444) ዐማርኛው “ማለደ” አሻሚነት ቢኖረው እንኳ፥ ሳያጣሩ “አብአማላጅተብሏል” ከማለት በፊት ቃሉ በሌሎች ቋንቋዎች ምን እንደ ተባለ ማመሳከር ይገባ ነበር። ለምሳሌ፡-  እንግሊዝኛው  “…  daily  rising  up  early…”  (KJV)  ይላል። የግእዙም ትርጕምእንዲህ  ነው  የሚለው  “አባቶቻቸው  ከግብጽ ምድር  ከወጡበት ቀን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ፤ በቀንናበሌሊት ባሪያዎቼን ነቢያትን ሁሉ ልኬባቸው ነበር፤” (2000 ሺህ ዕትምሁለቱም በጥዋትመነሣትን ወይም ጊዜን እንጂ ምልጃን
ወይም ልመናን አያሳዩም።መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት የሌለውን የራስን ሐሳብ በእግዚአብሔር ቃልከማረምከማስተካከል  ይልቅ  ቃሉን  ለማጣመም  መሞከር  የእግዚአብሔር  ሳይሆን  የሰውአገልጋይ  መሆን  ነው፤  እውነተኛ  ሰባኪ  ግን  እግዚአብሔርን  እንጂ  ሰውን  ደስ ለማሰኘት አይሰብክም  (ገላ.  110)  አለአግባብ  ተጠቅሶ  በተሳሳተ  መንገድ የተተረጐመው  ይህ  ጥቅስ ለተከራካሪዎቹ  የማስተዛዘኛ  ውጤት  እንኳ እንዳላስገኘላቸው ግልጽ ነው።
(((((((((((“መንፈስ ቅዱስም ይማልዳል ተብሏልና ወደማን ይማልዳል?” ))))))))))))
እንዲሁም ደግሞ መንፈስ ድካማችንን ያግዛል፤ እንዴት እንድንጸልይ እንደሚገባን አናውቅምና፥ ነገር  ግን  መንፈስ  ራሱ  በማይነገር  መቃተት  ይማልድልናል፤ ልብንም  የሚመረምረው የመንፈስ  አሳብ  ምን  እንደ  ሆነ  ያውቃል፥  እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ስለ ቅዱሳን ይማልዳልና” (ሮሜ 826-27) ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ  መንፈስ  ቅዱስን  “ሌላ  አጽናኝ”  ሲል  ጠርቶታል (ዮሐ.  1415-16 እንዲሁም  ቊጥር  26  1526  167  ይመለከቷል)  ሌላ  አጽናኝ ያለውም ኢየሱስ ወደ ሰማይ ካረገና በአብ ቀኝ ከተቀመጠ በኋላ፥ እርሱን ተክቶ የሚሠራ፥ ማለትም፦ ከደቀ  መዛሙርቱ  ጋር  የሚኖር፣  ሁሉን  የሚያስተምርና  ኢየሱስ የተናገረውን የሚያሳስብ፣ ስለኢየሱስ የሚመሰክር፣ ስለ ኀጢአት፣ ስለ ጽድቅና ስለ ፍርድ  ዓለምን  የሚወቅሥ  ሌላው  የሥላሴ አካል  ነው።    ኢየሱስ  እኔ  ብሄድ ይሻላችኋል፤ እኔ ካልሄድሁ አጽናኙ አይመጣም ሲል፥የሚመጣው አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ፥  ከአብ  የሚወጣ  የሥላሴ አንዱ አካል መሆኑን ያስረዳል።ኢየሱስን ሊተካ የሚችል፥  እንደ  እርሱ ያለ መንፈስ ቅዱስ  ነው  እንጂ ሌላ ፍጡር ሊሆን  በፍጹምአይችልም።ስለ ሌላ አጽናኝ የተናገረውም፥ እርሱ ከደቀ መዛሙርቱ ተለይቶ የሚሄድበት ሰዓትመድረሱን ሲነግራቸው  የደቀ መዛሙርቱ ልብ  በሐዘን መታወኩን ተከትሎ  ነው። በጊዜው  በሥጋ ዐብሮአቸው  የነበረውና  ስፍራን  ሊያዘጋጅላቸው  ወደ  ሰማይ የሚሄደው  መምህራቸው  ኢየሱስ በሥጋ  ከእነርሱ  ተለይቶ  ከሄደ  በኋላ  ተመልሶ መጥቶ  ወደ  እርሱ  እስኪወስዳቸው  ድረስ፥  እንደ እርሱ  ያለ  ሌላ  አጽናኝ እንደሚመጣ ነው የነገራቸው (ዮሐ. 141-313-17) እርሱም መንፈስቅዱስ ነው። ከላይ በተጠቀሱት የዮሐንስ ወንጌል ክፍሎች (ዮሐ. 1415-1626 1526 167)
አጽናኝ” ተብሎ  የተተረጐመው ቃል  በግሪኩ  “ጰራቅሊጦስ”  የሚለው ቃል  ነው።ጰራቅሊጦስማለትም፦ አማላጅ፣ ጠበቃ፣ አጽናኝ ማለት ነው። ቃሉ ለመንፈስ ቅዱስተቀጽሎ  ስለሚገኝ  መንፈስ ቅዱስ  ስለ  ቅዱሳን  ይማልዳል  የሚለው  ትምህርትመንፈስ  ቅዱስን  ዝቅ  ማድረግ  አይሆንም። ከላይ  ስለ  አብ  በተናገርንበት  ክፍልየተሰጠው ማብራሪያ  እዚህ  ላይ  ለመንፈስ ቅዱስምይሠራል።   ኢየሱስ  በሥጋውወራት  ለደቀ  መዛሙርቱ  ይማልድ  እንደ  ነበረ፥  እርሱ  ወደ  ሰማይ ካረገ  በኋላ የወረደውና  ከላይ  የተዘረዘሩትን  ታላላቅ  መንፈሳውያን  ተግባራትን  ለቤተ ክርስቲያንእያከናወነ ያለው መንፈስ ቅዱስ፥ ቅዱሳንን (ምእመናንንበድካማቸው ጊዜ ያግዛቸዋል፤ እንደእግዚአብሔር ፈቃድም ይማልድላቸዋል። ይህ እንዴት ባለ ሁኔታ  ይከናወናል?  ቢባል  በቃላትመግለጽ  በማይቻል መቃተት መሆኑን  ቃሉያስረዳል። ይሁን  እንጂ  200 ሺሁ  ዕትም መጽሐፍ ቅዱስ፥ ይህን ሐሳብ  ለውጦ ይማልዳል የሚለውን ይፈርዳል ሲል ጽፏል፡፡ ይህም  ከቅርብ  ጊዜወዲህ  እየተስፋፋ  የመጣ የአንድ  ወገን  የአተረጓጐም  ባህል  ነው።  የግእዙ  ንባብ  ከሚለውውጪም  የተሰጠ ትርጓሜ  ነው።  በቅዱስ  ጳውሎስ  መልእክታት  አንድምታ  ትርጓሜ  ላይ  ግንይከራከራል”  ተባለ  እንጂ  “ይፈርዳል”  አልተባለም።  እነዚህ  ክፍሎች  ግን ከእግዚአብሔር ሐሳብይልቅ ለትርጓሜ ባህላቸው ሲሉ፥ “ወባሕቱ መንፈስ ለሊሁ ይትዋቀሥ ለነ በእንተ ሕማምነወምንዳቤነ - ነገር ግን ራሱ መንፈስ ቅዱስ ራሱ ስለ መከራችንና  ስለ  ችግራችን  ይከራከርልናል” (ሮሜ  826)  የሚለውን  “ይፈርዳል” ሲሉ ተርጕመዉታል። ይሁን እንጂ በዚህ የጳውሎስመልእክት ላይ ተመሥትረውሌሎች መጻሕፍት መንፈስ  ቅዱስ  ስለ  እኛ  እንደሚጸልይመስክረዋል።  አረጋዊ መንፈሳዊ  በተባለ  የመነኮሳት መጽሐፍ  ላይ  እንዲህ  ተጽፏል፤  “ወባሕቱ አጸምዖ ለመንፈስ  ዘኅዱር  ላዕሌየ ወአስተሔውዝ ኪያሁ  ውእቱ  ዘተብህለ ከመ መንፈሱ ይጼሊበእንቲኣነ  -  ነገር ግን በእኔ ዐድሮ የሚኖረውን የመንፈስ ቅዱስን  ነገር ብቻእሰማለሁ፤    በእርሱም አደንቃለሁ፤  ይህ  ‘መንፈስ  ቅዱስ  ስለ  እኛ  ይጸልያልየተባለው ነገር ነው።” (አረጋዊ መንፈሳዊድርሳን 13)

ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ (የዮሐንስ ወንጌል 1;12) This website was created for free with Own-Free-Website.com. Would you also like to have your own website?
Sign up for free