ONE BIBLE TRUTH /የእወነት ቃል /
ለፍጥረቱ የበኵራት ዓይነት እንድንሆን በእውነት ቃል አስቦ ወለደን

BIBLE TRUTH

ልዩ ወንጌል

 
     በቅድሚያ ልዩ ወንጌል” የተባለውምንድነውስለ ልዩ ወንጌል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥበገላትያ 1ላይ በክርስቶስ ጸጋ እናንተን ከጠራችሁከእርሱ ወደ ልዩ ወንጌል እንዲህ ፈጥናችሁ እንዴት


እንዳለፋችሁ እደነቃለሁ፤” ተብሎ ተጽፏል፡፡እንደዚሁም በ2ኛ ቆሮንቶስ 11ላይ የሚመጣውም ያልሰበክነውን ሌላ ኢየሱስ ቢሰብክ፥ ወይም
ያላገኛችሁትን ልዩ መንፈስ ወይም ያልተቀበላችሁትንልዩ ወንጌል ብታገኙ፥ በመልካም ትታገሡታላችሁ።ተብሎ ተጽፏል፡፡ ከእነዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የምንረዳው ልዩ ወንጌል ተብሎ የተገለጸው
ከእውነተኛውና የሚያድነውን የምሥራች ከያዘው ወንጌል በተቃራኒ የሚገኝና እውነተኛውን ወንጌል ለማስተባበል የሚሰበክና በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እውነተኛውን ወንጌል የሚቃወም መልእክት ነው፡፡ እንዲህ ያለው የተሳሳተልዩ ወንጌል” በሚያጋጥመን ጊዜ እንዳንቀበለውና
በመልካም እንድንታገሰው ሐዋርያው ጳውሎስ በሁለቱም ጥቅሶች ውስጥ አስተምሮናል፡፡
  እውነተኛው ወንጌል ስለኢየሱስ ክርስቶስ የሚናገርና መዳን በእርሱ በኩል ብቻ እንደሚገኝ የሚመሰክር ነው፡፡ ወንጌል ከዚህ ውጪ ሌላ መልእክት የለውም፡፡ ይህን ሐቅ ክዶ በሌላ ወገን ወይም በሌላ መንገድ መዳን እንደሚገኝ የሚሰብክ ሌላ መጽሐፍ ወይም ሰው ቢኖር መጽሐፉ ልዩ ወንጌል ሰውየውም የሐሰት አስተማሪ ነውና ሁለቱም የተወገዙ
 
ናቸው፡፡ ምክንያቱም ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመ ይሁን። አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት የተለየውን ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን።” ይላልና የእግዚአብሔር ቃል (ገላ. 18-9)፡፡
ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ (የዮሐንስ ወንጌል 1;12) This website was created for free with Own-Free-Website.com. Would you also like to have your own website?
Sign up for free